አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓመታዊው የ“አፔክስ” የመንገደኞች ምርጫ “ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ” ሽልማት አሸንፏል፡፡
አየር መንገዱ ሽልማቱን የተቀዳጀው በምርጥ የበረራ መስተንግዶ፣ መዝናኛ ፣ ምግብና መጠጥ፣ ምቾት እንዲሁም በገመድ ዓልባ የኢንተርኔት “ዋይ ፋይ”አገልግሎት ዘርፎች መሆኑን የአየር መንገዱ መረጃ ያመላክታል።
አየር መንገዱ ሽልማቱን የተቀበለው በአየርላንዷ ደብሊን በተዘጋጀ መርሐ-ግብር ነው፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!