Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በሱዳን የተኩስ አቁም ሥምምነቱ ለተጨማሪ 5 ቀናት ተራዘመ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 22 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)የሱዳን ተፋላሚ ኃይሎች የተኩስ አቁም ሥምምነቱን ለተጨማሪ 5 ቀናት አራዘሙት፡፡

የሱዳን ጦር እና የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሃይል አዲስ ስምምነት ላይ የደረሱት በፈረንጆቹ ግንቦት 20 ቀን 2023 በሳዑዲ አረቢያ መዲና ጅዳ ከመከሩ በኋላ መሆኑን ሺንዋ አል-አረቢያን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል፡፡

ሁለቱ ኃይሎች ሠላማዊ ዜጎች ከጦርነት ቀጣናው ለመውጣት የሚያደርጉትን ጥረት መንገድ በመክፈት ለማሳለጥ ሥምምነት ላይ መድረሳቸውም ነው የተመላከተው፡፡

ተፋላሚዎቹ ከጦርነት ቀጣናው ሸሽተው የሚወጡ ነዋሪዎች ያለ ሐሳብ ከጓዛቸው ጋር እንዲንቀሳቀሱ ሥምምነት ላይ ደርሰዋልም ነው የተባለው፡፡

የአሁኑ የአጭር ጊዜ የተኩስ አቁም ሥምምነት እና የሰብዓዊነት ምላሽ በፈረንጆቹ ግንቦት 6 ላይ በሳዑዲ እና በአሜሪካ አነሳሽነት የተጀመረው በሱዳን ዘላቂ ሠላም የማስፈን ጥረት ማሳያ ነው ተብሏል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version