Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ፖል ካጋሜ በመከላከያ እና በደኅንነት ባለሥልጣናት ላይ ድንገተኛ ለውጥ ማድረጋቸው ተሰማ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)የሩዋንዳ ፕሬዚደንት ፖል ካጋሜ የመከላከያ እና የደኅንነት ሚኒስትሮችና አዛዦች ለውጥ ማድረጋቸው ተሰማ::

ፕሬዚደንት ፖል ካጋሜ በለወጧቸው ባለሥልጣናት ምትክ ÷ ጆቪኔል ማሪዛሙንዳን በመከላከያ ሚኒስትርነት ፣ ሌተናል ጄነራል ሙባራክ ሙጋንጋን ደግሞ በመከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኤታማዦርነት ሾመዋቸዋል::

በተጨማሪም የሀገሪቱ የምድር ኃይል ዋና አዛዥ እና የመከላከያ ሠራዊቱ የመረጃና ደኅንነት በአዲስ አዛዥና ኃላፊ መተካታቸው ተሰምቷል፡፡

ሞዛምቢክን ለማገዝ በተሰማራው የሩዋንዳ ኃይል ላይም የአዛዦች ለውጥ ተደርጓል ነው የተባለው::

የሩዋንዳው ዘ ኒው ታይምስ እንደዘገበው ፥ ፕሬዚደንት ካጋሜ ባለፈው ሰኞ ምሽት ይፋ ያደረጉት ሹም-ሽር ያልተጠበቀና ድንገተኛ ነበር::

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version