Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2016 ዓ.ም ውድድር መስከረም 20 ይጀመራል

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር የ2016 ዓ.ም ውድድር መስከረም 20 ቀን እንደሚጀመር አስታውቋል፡፡

የ2015 ዓ.ም ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ሐምሌ 1 ቀን 2015 ዓ.ም መጠናቀቁ ይታወሳል፡፡

በቀጣይ የሚካሄደው የ2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድርም መስከረም 20 ቀን 2016 ዓ.ም እንዲጀመር መወሰኑን የአክሲዮን ማህበሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

የውድድር ዘመኑ  የሚጀምርበትን ቀን ተሳታፊ ክለቦች  እንዲያውቁ መደረጉ ተጠቁሟል፡፡

Exit mobile version