Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

መደመር መፅሃፍ በፋና ኤፍ ኤም 98 ነጥብ 1 ላይ ከዛሬ ጀምሮ በየዕለቱ ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ ይተረካል

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በፋና ኤፍ ኤም 98 ነጥብ 1 ላይ የመደመር መጽሐፍ በድምፅ እንደሚተረክ ገለፀ።

በጣቢያው ዛሬ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በየዕለቱ መደመር መፅሃፍ የሚተረክ ሲሆን፥ አድማጮች ይህን የመፅሃፍ ትረካ እንዲያደምጡ ጋብዟል።

በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የተፃፈው “መደመር” መፅሃፍ ባለፈው ጥቅምት ወር ነበር የተመረቀው።

Exit mobile version