Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በአዲስ አበባ ደርቢ ቡናማዎቹ ተጋጣሚያቸውን አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ደርቢ ኢትዮጵያ ቡና ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 በማሸነፍ ወሳኝ ሦስት ነጥብ አሳክቷል፡፡

9፡00 ላይ በተደረገው ተስተካካይ ጨዋታ የቡናማዎቹን ብቸኛ ጎል ጫላ ተሺታ ከመረብ አሳርፏል፡፡

በጨዋታው ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥብ ለመጋራት በተደጋጋሚ ያደረገውን ሙከራ ወደ ውጤት መቀየር ሳይችል ቀርቷል፡፡

ውጤቱን ተከትሎም ኢትዮጵያ ቡና በ11 ነጥብ 7ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ÷ ፈረሰኞቹ በ16 ነጥቦች በነበሩበት 4ኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ፡፡

Exit mobile version