Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

2023 ለሴቶች 5 ሺህ ሜትር ሩጫ ውድድር ታሪካዊ ዓመት ነበር ተባለ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የፈረንጆቹ 2023 ለሴቶች 5 ሺህ ሜትር ሩጫ ውድድር የተለየ ዓመት እና ታሪካዊ እንደነበረ የዓለም አትሌቲክስ ገለጸ።

በዓመቱ የርቀቱ ክብረ ወሰን ሁለት መሰበሩን ጠቅሷል።

ከዚህ በተጨማሪም የርቀቱ የምንጊዜም 10 ፈጣን ሰዓት መካከል ስድስቱ በዚህ ዓመት የተመዘገበ መሆኑን የዓለም አትሌቲክስ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባወጣው መረጃ አመልክቷል።

የርቀቱን የዓለም ክብረ ወሰን በአሜሪካ ኢውጅን በተካሄደው የዳይመንድ ሊግ ውድድር ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ 14 ደቂቃ ከ00 ሴኮንድ ከ21 ማይክሮ ሴኮንድ በመግባት በእጇ ማስገባቷ ይታወቃል።

 

 

Exit mobile version