አዲስ አበባ ፣ ታኅሣስ 26 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ9ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ፋሲል ከነማ እና ኢትዮጵያ ቡና ድል ቀንቷቸዋል።
ከቀትር በኋላ በተካሄደ ጨዋታ ፋሲል ከነማ ድሬዳዋ ከተማን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
የፋሲል ከነማን የማሸነፊያ ጎሎች ጌታነህ ከበደ እና ናትናኤል ገብረጊዮርጊስ አስቆጥረዋል፡፡
ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተካሄደ ጨዋታ ደግሞ ኢትዮጵያ ቡና ሃዋሳ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል።
የድል ጎሎቹን መስፍን ታፈሰ ሲያስቆጥር አቤኔዘር ዮሐንስ ደግሞ የሐዋሳ ከተማን የማስተዛዘኛ ጎል አስቆጥሯል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!