Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አቶ ሙስጠፌ በደገሀቡር ከተማ በግንባታ ላይ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሐመድ በጀረር ዞን ደገሀቡር ከተማ አስተዳደር እየተካሄዱ የሚገኙ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች የሥራ ሂደት ተመልክተዋል።

በጉብኝታቸውም ግንባታቸው እየተከናወኑ የሚገኙ 4 ነጥብ 1 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ የመንገድ ፣ የደገሀቡር ሆስፒታልን የማስፋፊያ፣ የደገሀቡር ከተማ እስታዲየም እና የከተማውን የንፁህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክት ግንባታ ሂደትን ተመልክተዋል፡፡

የመንገዶቹ ግንባታ እየተከናወነ የሚገኘው በከተማ ልማትና ግንባታ ቢሮ እንዲሁም በደገሀቡር ከተማ አስተዳደር አማካኝነት መሆኑን የክልሉ መገናኛ ብዙኃን ዘግቧል፡፡

የሆስፒታሉ ማስፋፊያ ግንባታው ሲጠናቀቅ 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ሰዎችን የማገልገል አቅም እንደሚኖረው ተጠቅሷል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ ከጉብኝታቸው በኋላ ከከተማዋ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጋር መወያየታቸው ተመላክቷል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version