Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በአፍሪካ ዋንጫ ሴኔጋል ጋምቢያን 3 ለ 0 አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታ ሴኔጋል ጋምቢያን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡

የሴኔጋልን የማሸነፊያ ግቦች ፔፔ ጉዮ እና ላሚን ካማራ አስቆጥረዋል፡፡

በጨዋታው የጋምቢያው ተከላካይ ኢብራሂማ አዳምስ በፈፀመው ያልተገባ ባህሪ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል፡፡

የአፍሪካ ዋንጫ መርሐ ግብር ምሽት መካሄዱን ሲቀጥል ምሽት 2 ሰዓት ካሜሩን ከጊኒ እንዲሁም ምሽት 5 ሰዓት አልጀሪያ ከአንጎላ ይጫወታሉ፡፡

Exit mobile version