Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አትሌት ለሜቻ ግርማ በፈረንሳይ ሌቪን በሚካሄደው የ3 ሺህ ሜትር ውድድር ይሳተፋል

አዲስ አበባ፣ ጥር 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ክብረ ወሰን ባለቤት ለሜቻ ግርማ በፈረንሳይ ሌቪን በሚካሄደው የ3 ሺህ ሜትር ውድድር እንደሚሳተፍ ተገለፀ፡፡

አትሌቱ ባለፈው የውድድር ዘመን በፈረንሳይ ሌቪን በ3 ሺህ ሜትር የቤት ውስጥ ውድድር በ7 ደቂቃ 23 ሰከንድ 81 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ሪከርድ ማሻሻሉ የሚታወስ ነው፡፡

ክብረወሰኑ ለ25 ዓመታት በኬንያዊው አትሌት ዳንኤል ኮመን ተይዞ መቆየቱም አይዘነጋም፡፡

የፈረንሳይ ሌቪን የቤት ወስጥ ውድድር የካቲት 10 የሚደረግ ሲሆን አትሌት ለሜቻ ከዚህ ወድድር ቀደም ብሎ በቦስተን የኒው ባላንስ የቤት ውስጥ ውድድር ጥር 18 እንደሚሳተፍም ተመላክቷል፡፡

በወርቅነህ ጋሻሁን

Exit mobile version