Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በጤና ተቋማት የሚሰሩ 65 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው ሚኒስትሯ አስታወቁ

ADDIS ABABA, ETHIOPIA - APRIL 27: Lia Tadesse, Health Minister of Ethiopia, speaks to press members as breathing apparatus brought by Ethiopian Airlines from different countries, are being delivered to Ethiopian Health Ministry with a ceremony at Bole International Airport in Addis Ababa, Ethiopia on April 27, 2020. (Photo by Minasse Wondimu Hailu/Anadolu Agency via Getty Images)

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 26/2012(ኢዜአ) በኢትዮጵያ እስካሁን ባለው ሂደት 49 የጤና ባለሙያዎችና 16 ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ገለጹ።

ባለሙያዎቹ በአብዛኛው በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የጤና ተቋማት እየሰሩ የነበሩ መሆናቸውን ገልፀዋል።

የጤና ባለሙያዎችና የጤና ተቋማት ሠራተኞች የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት እያደረጉት ላለው ተጋድሎም ምስጋና አቅርበዋል።

መንግሥት የጤና ተቋማት ሠራተኞችን ተጋላጭነት ለመቀነስ ከሚያደርገው ሥራ በተጨማሪ ኅብረተሰቡ ራሱን በመጠበቅ የባለሙያዎቹን ጫና እንዲቀንስም ጠይቀዋል።

ከዚህ ጋር ተያይዞ በተለይ ማህበረሰቡ የቫይረሱን ስርጭት የሚመጥን ጥንቃቄ አለመደረጉ እንደሚያሳስባቸው ሚኒስትሯ ተናግረዋል።

“ጥንቃቄ የምናደርገው የጸጥታ አካላት ወይም የጤና ባለሙያዎችን ትዕዛዝ ለማክበር ሳይሆን፤ ለራሳችንና ለምንወዳቸው ወገኖቻችን ብለን መሆን አለበት” ሲሉም ምክራቸውን አስተላልፈዋል።

ምንጭ፡- ኢዜአ

Exit mobile version