Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ርዕሰ መሥተዳድር ጥላሁን ከባስኬቶ ዞን ነዋሪዎች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ጥላሁን ከበደ ከባስኬቶ ዞን ነዋሪዎች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡

በውይይታቸውም÷ ዞኑ ጤፍ፣ በቆሎ፣ ሰሊጥ፣ ሩዝ፣ ኮረሪማና ሌሎች የግብርና ምርቶችን በብዛት አምራች ቢሆንም ምርቶችን ወደ ገበያ ለማውጣት የመንገድ ችግር መኖሩን ተሳታፊዎች አንስተዋል፡፡

በተጨማሪም የንጹህ የመጠጥ ውኃና የኤሌክትሪክ አቅርቦት ችግርን ጨምሮ ሌሎች አሉ ያሏቸውን ችግሮች ገልጸዋል፡፡

ርዕሠ መሥተዳድሩ በሰጡት ምላሽም÷ ክልሉ የሰላም፣ የመቻቻል እና የብልፅግና ተምሳሌት እንዲሆን ባለፉት 6 ወራት በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ገልጸዋል፡፡

በዞኑ ተስፋ ሰጪ ለውጦች እየታዩ መሆናቸውን ጠቅሰው÷ በተሳታፊዎች የተነሱትን ጥያቄዎች ጨምሮ ሌሎች ጉዳዮችንም ቅድሚያ የሚሰጠውን በማስቀደም ችግሮችን በሂደት ለመፍታት እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡

በኢብራሂም ባዲ

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version