Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አትሌት ሳሙኤል ፍሬው በ3 ሺህ ሜትር መሰናከል የመጀመሪያውን ወርቅ ለሀገሩ አስገኘ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ13ኛው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ወንዶች አትሌት ሳሙኤል ፍሬው የመጀመሪያውን ወርቅ ለኢትዮጵያ አስገኝቷል፡፡

አትሌት ሳሙኤል ርቀቱን 8 ደቂቃ 24 ሰከንድ ከ30 ማይክሮ ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ነው ቀዳሚ የሆነው፡፡

በመርሐ ግብሩ የ5 ሺህ ሜትር የሴቶች ፍፃሜ ውድድር ሲካሄድ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች እንደሚጠበቁ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version