Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

1 ሺህ 71 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሦስት ዙር በተከናወነ በሳውዲ ዓረቢያ ችግር ውስጥ የነበሩ ዜጎችን የመመለስ ሥራ 1 ሺህ 71 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ፡፡

በዛሬው ዕለት ወደ ሀገር የተመለሱት 1 ሺህ 71 ዜጎች ሁሉም ወንዶች ሲሆኑ ፥ ዘጠኙ ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ናቸው ተብሏል።

ለተመላሽ ዜጎች በአውሮፕላን ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ በማድረግ ከቤተሰብ ጋር የመቀላቀል ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version