አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 18፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ ) አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተለያየ መስኮች ያስተማራቸውን ከ5 ሺህ 600 በላይ ተማሪዎችን አስመረቀ፡፡
ከተመራቂዎቹ መካከል 244 በሶስተኛ ዲግሪ፣ 3 ሺህ 128 በ2ኛ ዲግሪ እንዲሁም 2 ሺህ 370 በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቁ ናቸው፡፡
ተመራቂዎቹ ወቅታዊ የጤና ስጋት በሆነው ኮቪድ19 ሳቢያ በቴሌቪዥን እና በዩኒቨርሲቲው ማህበራዊ የትስስር ገጽ በተላለፈ ስነ ስርአት ነው የተመረቁት፡፡