Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በአዲስ አበባ ተጨማሪ 674 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል

አዲስ አበባ ፣ ነሃሴ 11 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ባለፉት 24 ሰዓታት ለ5 ሺህ 641 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርግ 674 ሰዎች ቫይረሱ እንደተገኘባቸው የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡

ከዚህ ባለፈም ባለፉት 24 ሰአታት የ14 ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 8 ከአስከሬን ምርመራ እንዲሁም ስድስቱ ከጤና ተቋም መሆኑንም ቢሮው አስታውቋል፡

እስከዛሬ ድረስ በከተማዋ ለ324 ሺህ 41 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 19 ሺህ 881 ደርሷልም ነው ያለው፡፡

Exit mobile version