Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በሁለት የአፍርካ ሀገራት የሚያደርጉትን ጉብኝት ጀምረዋል

ABIDJAN, IVORY COAST - DECEMBER 20: French President Emmanuel Macron and his wife Brigitte Macron are being welcomed by President of Ivory Coast Alassane Ouattara and his wife Dominique Folloroux-Ouattara with an official welcoming ceremony at the Felix Houphouet Boigny International Airport in Abidjan, Ivory Coast on December 20, 2019. (Photo by Cyrille Bah/Anadolu Agency via Getty Images)

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 11፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በሁለት የአፍርካ ሀገራት የሚያደርጉትን ጉብኝት በዛሬው እለት ጀምረዋል።

ፕሬዚዳንቱ በአይቮሪ ኮስት እና በኒጄር ይፋዊ የስራ ጉብኝት የሚያደርጉ ሲሆን፥ በትናንትናው ምሽትም አይቮሪ ኮስት መግባታቸው ነው የተነገረው።

በአይቮሪ ኮስት ቆይታቸውም በምእራብ አፍሪካ ቀጠና የሚገኙ ጂሃዲስት ሀይሎችን እየተዋጋ ከሚገኘው የፈረንሳይ ጦር ጋር የበዓል ምግብ መመገባቸውም ታውቋል።

በተጨማሪም በአርቮሪኮስት የፈረንሳይ ወታደራዊ ማዘዣ ጣቢያ በመገኘትም ከሁሉም የሀገሪቱ ጦር አባላት ጋር ውይይት ማድረጋቸው ነው የተነገረው።

ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በአይቮሪ ኮስት ቆይታቸውም ሽብርተኝነትን መዋጋት ላይ ዓላማ ያደረገ ዓለም አቀፍ አካዳሚ ለማቋቋም ድጋፍ እንደሚያደርጉም ይጠበቃል።

በነገው እለትም ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ወደ ኒጀር ያቀናሉ የተባለ ሲሆን፥ በቆይታቸውም ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ማሃሙዱ ኢሶፉ ጋር ተገናኝተው እንደሚወያዩም ይጠበቃል።

ምንጭ፦ africa.cgtn.com

Exit mobile version