Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ዋልያዎቹ በቀጣይ ሳምንት ከዛምቢያ ጋር የወዳጅነት ጨዋታ ያደርጋሉ

Zambia's Collins Mbesuma during the 2013 Africa Cup of Nations soccer match, Zambia vs Ethiopia at The Giraffe Stadium in Mbombela on January 21, 2013. The match ended in a 1-1 draw. Photo by Christian Liewig/NCI/ABACAPRESS.COM | 349263_047

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ወንዶች ብሄራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) በቀጣይ ሳምንት ከዛምቢያ አቻው ጋር የወዳጅነት ጨዋታ እንደሚያደርጉ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ።
 
የወዳጅነት ጨዋታው ጥቅምት 12ና 15 ቀን 2013 በአዲስ አበባ ስታድየም እንደሚካሄድ ነው የተገለፀው።
 
ብሄራዊ ቡድኑ ለአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ዝግጅቱን በካፍ አካዳሚ እያከናወነ የሚገኘ ሲሆን ከኒጀር ጋር ከሚያደርገው የደርሶ መልስ ጨዋታ በፊት ነው የወዳጅነት ጨዋታውን የሚያከናውነው።
Exit mobile version