Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ሀዋሳ ከተማ ኤፍሬም አሻሞን አስፈረመ

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 16 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስመር አጥቂው ኤፍሬም አሻሞ ከመቐለ 70 እንደርታ ወደ ሀዋሳ ከተማ በአንድ አመት ውል ተዘዋውሯል፡፡

በቀድሞ ተጫዋቹ ሙሉጌታ ምህረት የሚሰለጥነው ሃዋሳ ከኤፍሬም አሻሞ በተጨማሪም ከደቡብ ፖሊስ ተከላካዩ ዘነበ ከድር እና ግብ ጠባቂውን ዳግም ተፈራ (ቻቺ) በአዲስ ውል ፈርመው ውላቸው ፀድቋል፡፡

በተመመሳሳይ ክለቡ ሰሞኑን የበርካታ ተጨዋቾችን ውል ያራዘመ እና አዲስ ተጨዋቾች ማስፈረሙን ከኢትዮ ኪክ ኦፍ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

Exit mobile version