Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ተመስገን ዳና የኢትዮጵያ ወጣቶች ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ በመሆን ተሾሙ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 20፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አሰልጣኝ ተመስገን ዳና የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ወንዶች ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ በመሆን ተሾሙ።

አሰልጣኝ ተመስገን ዳና የአንድ ዓመት ውል ኮንትራት ቀርቦላቸው ፊርማቸውን አኑረዋል፡፡

አሰልጣኙ በሴካፋ ተፎካካሪ እና ውጤታማ ቡድን እንዲሰሩ ግዴታ እንደተጣለባቸው ከፌዴሬሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ከዚህ ቀደም ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በመያዝ በሴካፋ የፍጻሜ ተፋላሚ ማድረጋቸው የሚታወስ ነው።

Exit mobile version