Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ዋልያዎቹ በኒጀር አቻቸው 1 ለ 0 ተሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 4፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ዋልያዎቹ በኒጀር አቻቸው 1 ለ 0 ተሸነፉ::

የኢትዮጵያ የወንዶች ብሄራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ሶስተኛ ጨዋታቸውን ዛሬ ምሽት ከኒጀር ጋር በኒያሚው ስታድ ጀነራል ሴኒ ስታዲየም አድርገዋል፡፡

በጨዋታው ኒጀሮች ያገኙትን የፍፁም ቅጣት ምት በማስቆጠር አሸናፊ ሆነዋል፡፡

ኢትዮጵያ በምትገኝበት ምድብ አይቮሪ ኮስት ከማዳጋስካር ያደረጉት ጨዋታ በአይቮሪኮስት 2 ለ 1 አሸናፊነት መጠናቀቁ የሚታወስ ነው።

Exit mobile version