Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የትራንስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት የአዋሽ ኮምቦልቻ ሃራ ገበያ የባቡር መንገድን በተመለከተ ከግንባታ ተቋራጩ አመራሮች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የትራንስፖርት ሚኒስትር ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ የአዋሽ ኮምቦልቻ ሃራ ገበያ የባቡር መንገድ ፕሮጀክት ግንባታን በተመለከተ ከግንባታ ተቋራጩ ያፒ ሜርኬዚ አመራሮች ጋር ተወያዩ።
ሚኒስትሯ የአዋሽ ኮምቦልቻ ሃራ ገበያ የባቡር መንገድን ግንባታ ቀሪ ስራዎችን በተመለከተ ከአመራሮቹ ጋር ውይይት አድርገዋል።
በዚህ የባቡር ፕሮጀክቱን በስኬት ለማጠናቀቅ በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ምክክር ማድረጋቸውን ሚኒስትሯ በትዊተር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል።
Exit mobile version