Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የቁም እንስሳት ነጋዴዎች ማህበር ከ4 ሚሊየን በላይ የሚገመት ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 15፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ባቀረቡት የድጋፍ ጥሪ መሰረት የቁም እንስሳት ነጋዴዎች ማህበር ከ4 ሚሊየን በላይ የሚገመት ድጋፍ አደረገ፡፡

ማህበሩ 160 ሰንጋዎችን ጨምሮ 2 ሺህ ሊትር ዘይት ነው ድጋፍ ያደረገው፡፡

ይህም በገንዘም ሲሰላ ከ4 ሚሊየን በላይ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ድጋፉን በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የከተማ ስራ አስኪያጅ ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ ተረክበዋል፡፡

ድጋፉን በተረከቡበት ወቅት እንዳሉት÷ መንግስት የጀመረው ህግን የማስከበር ዘመቻ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እና ህብረተሰቡም የቻለውን እንዲያደርግ እና እያደረገ ያለው ድጋፍ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በፈቲያ አብደላ

Exit mobile version