Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የጊኒ ዎርምን ለማጥፋት በሚቻልበት አግባብ ላይ የሚመክር መድረክ እየተካሄደ ነው

አበባ፣ ህዳር 16፣ 2013 (ኤፍቢሲ) በኢትዮጵያ የጊኒ ዎርምን ማጥፋት በሚቻልበት አግባብ ላይ የሚመክር መድረክ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

መርሃ ግብሩ ለሁለት ቀናት እንደሚቆይ የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታውቀዋል፡፡

በመድረኩ ጊኒ ዎርምን ለማጥፋት ዋና ዋና ተግዳሮቶች እንደሚለዩም ገልጸዋል፡፡

እንዲሁም የባለድርሻ አካላት ተሳትፎና ሁለገብ ትብብርን ይበልጥ በማጠናከር በሽታውን ጨርሶ ከኢትዮጵያ ለማጥፋት የሚያስችሉ አዳዲስ ስትራቴጂዎችን በመንደፍ ላይ እንደሚያተኩሩ በፌስ ቡክ ገጻቸው አስፍረዋል፡፡

 

Exit mobile version