Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የወልቃይት፣ ጠገዴ እና ዳንሻ ከተማ ነዋሪዎች ከሃዲው የትህነግ ቡድን መደምሰሱን ተከትሎ ደስታቸውን እየገለፁ ነው

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 20 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የወልቃይት፣ ጠገዴ እና ዳንሻ ከተማ ነዋሪዎች ከሃዲው የትህነግ ቡድን መደምሰሱን ተከትሎ ደስታቸውን እየገለፁ ይገኛሉ፡፡
ነዋሪዎቹ ለጀግናው የመከላከያ ሰራዊት፣ ለአማራ ልዩ ኃይል እና ሚሊሻ የድጋፍ ሰልፍ እያካሄዱ ነው፡፡
በዚህ ወቅት የከተማው ነዋሪዎች አማራ በመሆናችን ብቻ ለ30 ዓመታት ሲደርስብን የነበረው ግፍ በማብቃቱ ነፃነታችንን በአደባባይ ለመግለፅ በቅተናል ብለዋል፡፡
ህዝቡ ለሰሜን እዝ አምስተኛ ሜካናይዝድ ክፍለ ጦር ያለውን ፍቅርም እየገለፀ እንደሚገኝ አብመድ ዘግቧል፡፡
Exit mobile version