Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ በጅቡቱ የሚገኙ የሎጀስቲክ መሰረተ ልማቶችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 21፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በጅቡቱ የሚገኙ የሎጀስቲክ መሰረተ ልማቶችን ጎበኙ።

በዚህ ወቅት ፕሬዚዳንቷ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ወሳኝ የሆነውን የሎጀስቲክ መሰረተ ልማት አቅም ማሻሻል የሚቻልበትን ሁኔታ በተመለከተ ውይይት አድርገዋል።

ለሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት በትናትናው ዕለት ጅቡቲ የገቡት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ  ከፕሬዚዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌ ጋር ውይይት ማድረጋቸው የሚታውስ ነው።

በተመሳሳይ በዛሬው ዕለትም በጅቡቲ ብሄራዊ ምክር ቤት በመገኘት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በተመለከተ ንግግር አድርገዋል።

Exit mobile version