Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ መተከል ዞን ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች የዕለት ደራሽ እርዳታ እየቀረበ እንደሚገኝ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች የዕለት ደራሽ እርዳታ እየቀረበ እንደሚገኝ ተገለጸ።

በክልሉ በመተከል ዞን በተከሰተው የፀጥታ ችግር ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች የዕለት ደራሽ እርዳታ እየተዳረሰ እንደሚገኝ ተገልጿል።

በዞኑ በተመረጡ ቦታዎች ማለትም ማንዱራ፣ ጉባ፣ ድባጤ፣ ጋሊሴ፣ ቡለን፣ ዳንጉር እና ወንበራ ላይ ካምፖች ተመስርተው የዕለት ደራሽ እርዳታ በመከፋፈል ላይ እንደሚገኝ የሰላም ሚኒስቴር ገልጿል።

Exit mobile version