Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጋና በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የብሄራዊ ቡድን አሰልጣኞችን አሰናበተች

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 24፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የጋና እግር ኳስ ማህበር በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የብሄራዊ ቡድን የአሰልጣኝ አባላት ማሰናበቱን አስታወቀ።

ማህበሩ የወንዶችና የሴቶች ብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ እና ረዳቶቻቸውን ከስራ ማሰናበቱን አስታውቋል።

ስንበቱ በሁለቱም ጾታዎች የታዳጊ፣ ወጣትና ዋናውን ቡድን አሰልጣኞችና ረዳቶቻቸውን ያካተተ ነው።

ማህበሩ የአሁኑ ስንብት እያደረገ ያለው ማሻሻያ አካል መሆኑን ገልጿል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ

Exit mobile version