Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ሰባት የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው ግለሰቦች በባዛሮች ጥራታቸውና ፈዋሽነታቸው ያልተረጋገጡ ምርቶችን ሲሸጡ በቁጥጥር ስር ዋሉ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 26፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)ሰባት የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው ግለሰቦች በባዛሮች ጥራታቸውና ፈዋሽነታቸው ያልተረጋገጡ ምርቶችን ሲሸጡ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በመተባበር ስምንት ዓይነት ያህል የባህላዊ መድኃኒቶች ጸጉርን ለማከምና ለማሳጅ ይረዳል በሚል ሲሸጡ በመገኘታቸው በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተጠቁሟል፡፡

በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እነዚህ ምርቶች ያልተመዘገቡ፣ የማይታወቁ ፣ጥራትና ደህነንነታቸው ያልተረጋገጠ በመሆኑ ህብረተሰቡ እንዳይጠቀም አሳስቧል፡፡

ባለስልጣኑ በድንገተኛ ቁጥጥሩ ወቅት የያዛቸው እና ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው ያሳሰበው ምርቶችም የሚከተሉት ናቸው፦

ካስቱሪር ሄርባል ሄር ( KASTURIR HERBALHAIR )

ንላንባሪ ካስቱራ ሄርባል ( NEELAMBARI KASTURA HERBAL )

ንላምባሪ ሄርባል ኦይል ( NEELAMBARI, HERBAL OIL )

ካስቱሪ ሄርባል ሄር ኦይል ( KASTURI HERBAL HAIR OIL)

ንላምባሪ ሄርባል ( NEELAMBARI, HERBAL)

ኤች ኤች አይ ኤን ኬ ኤን አይ ( HHINKNI)

ሳንጂቪን ሄርባል አዩስቸር ( SNNSEV,N HYREBALE Ayu)

ንላምባሪ ሄርባል ማሳጅ ( NEELAMBARI,HERBAL MASSAGE)

Exit mobile version