Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ፖሊስ ለበዓሉ በቂ ዝግጅት ማድረጉን ገለፀ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 27፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የገና በዓል በሰላም እንዲከበር በቂ ዝግጅት ማድረጉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።

በኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነትና የሚዲያ ሀላፊ ዋና ኢንስፔክተር ማርቆስ ታደሰ ለጣቢያችን እንደተናገሩት፥ ፖሊስ ኮሚሽኑ ለበዓሉ በቂ ዝግጅት አድርጓል።

የፖሊስ አባላትም ሰዎች በሚበዙባቸው የግብይት ቦታዎች እና የትራፊክ ፍሰት በሚበዛባቸው አካባቢዎች ተሰማርተዋል ነው ያሉት።

በተለይም ስርቆት፣ ቅሚያ፣ ማታለል እና ባዕድ ነገር ከምግብ ጋር ቀላቅሎ መሸጥ በበዓል ግብይት ጊዜ ሊከሰቱ የሚችሉ ወንጀሎች በመሆናቸው ህብረተሰቡ ለግብይት ሲወጣ ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስበዋል።

በጌታሰው የሺዋስ

Exit mobile version