Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በአማራ ክልል ለ54 ከተሞች ሽግግር ተፈቀደ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 22፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) ከተሞችን የእድገት ማዕከል ለማድረግ ለ54 ከተሞች ሽግግር መፈቀዱን የአማራ ክልል ከተማ ልማትና ቤቶች ኮንስትራክሽን ቢሮ ገለጸ።

በምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ደረጃ የአማራ ክልል ከተማ ልማትና ቤቶች ኮንስትራክሽን ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ሰዒድ ኑሩ እንደገለጹት፤ ከተሞችን የብልጽግና ማዕከል ማድረግ አንደኛው ሥራ ነው፡፡

በከተሞች ሀብት መፍጠር፣ ከተሞች ለነዋሪዎች ምቹ እንዲሆኑና የስልጣኔ ማዕከል ለማድረግ እየተሠራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

ለ54 ከተሞች ሽግግር መፈቀዱን የጠቀሱት ዶክተር ሰኢድ የክልሉ መንግሥት ቢሮው ያቀረበለትን ጥያቄ መቀበሉን ጠቅሰዋል፡፡

በዚህ ሂደትም ለታዳጊ ከተማነት ከገጠር ማዕከል 10፣ ከታዳጊ ከተሞች ወደ ንዑስ ማዘጋጃ ቤት 10፣ ከንዑስ ማዘጋጃ ቤት ወደ መሪ ማዘጋጃ ቤት አራት እና ከመሪ ማዘጋጃ ወደ ከተማ አስተዳደርነት 30 ከተሞች መሸጋገራቸውን አብመድ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version