Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ወልቂጤ ከተማ ጅማ አባ ጅፋርን 2 ለ 1 አሸነፈ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 27 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ወልቂጤ ከተማ ከጅማ አባ ጅፋር በባህርዳር አለም አቀፍ ስታድየም ያደረጉት ጨዋታ በወልቂጤ አሸናፊነት ተጠናቋል።

ጅማ አባ ጅፋሮች ተመስገን ደረሰ ጨዋታው በጀመረ በ4ኛው ደቂቃ ላይ ቀዳሚ ቢያደርጋቸውም ሰራተኞቹ ከእረፍ መልስ ባስቆጠሯቸው ግቦች ማሸነፍ ችለዋል።

የወልቂጤ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች አሜ መሀመድ በ63ኛው እና አህመድ ሁሴን በ70ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥረዋል።

በተካታታይ ጨዋታዎች ነጥብ ሲጥሉ የነበሩት ወልቂጤዎች ደረጃቸውን ከ8ኛ ወደ 6ኛ አሻሽለዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version