Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ስልጣናቸውን በቀጣዩ ወር የሚለቁት የኒጀር ፕሬዚዳንት የ5 ሚሊየን ዶላር ሽልማት አሸነፉ

Niger's President Mahamadou Issoufou speaks during an interview at the presidential palace in Niamey, on July 6, 2019. - The launch of an African Continental Free Trade Area (AfCFTA) will be the focus of the two-day summit in the capital Niamey. Heads of state will meet for an African Union (AU) summit in Niger on July 7 to usher in a landmark free trade agreement and consider looming security and migration crises. (Photo by ISSOUF SANOGO / AFP) (Photo credit should read ISSOUF SANOGO/AFP/Getty Images)

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ከሁለት ዙር የስልጣን ዘመን በኋላ ስልጣናቸውን በቀጣዩ ወር የሚለቁት የኒጀሩ ፕሬዚዳንት መሀመዱ የሱፍ የ2020 የአለም ትልቁን የመሪዎች ሽልማት አሸነፉ።

በዚህም በሱዳናዊው ቢሊየነር የተቋቋመውን የሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን ሽልማት በማሸነፋቸው 5 ሚሊየን ዶላር ይበረከትላቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።

በአፍሪካ የመልካም አስተዳደር ለማሻሻል በ2006 የተቋቋመው ፋውንዴሽኑ የኒጀሩን ፕሬዚንዳንት ጨምሮ ስልጣናቸውን በሰለማዊ መንገድ ለቀቁ ስድስት የአፍሪካ መሪዎች ሽልማቱን ሰጥቷል።

የፋውንዴሽኑ ሊቀመንበር ሞጌይ ፕሬዚዳንቱ ሀገራቸው በብዙ ፈተናዎች ውስጥ ሆናም ህዝባቸውን በለውጥ ጎዳና ወስደዋል ማለታቸውን ብሎበርግ አፍሪካ ዘግቧል።

ፕሬዚዳንቱ በበኩላቸው ይህ ሽልማት በኒጀር ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ዲሞክራሲን እና መልካም አስተዳደርን ለማስተዋወቅ እንዲሰሩ እንደሚያበረታታቸው ተናግረዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

Exit mobile version