Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አምባሳደር ሄኖክ ተፈራ ከፈረንሳይ መከላከያ ሚኒስቴር ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ሃላፊ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 1 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በፈረንሳይ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሄኖክ ተፈራ ከፈረንሳይ መከላከያ ሚኒስቴር ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ሃላፊ ሜጀር ጄኔራል ሎረን ማርበፍ ጋር ተወያዩ፡፡

በወቅቱም በሁለቱ ሃገራት የጋራ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን አምባሳደር ሄኖክ አስታውቀዋል፡፡

ከዚህ ባለፈም በሁለቱ ሃገራት ወቅታዊ ጉዳዮች ላይም ሃሳብ ተለዋውጠዋል፡፡

በተጨማሪም ፈረንሳይ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ወታደራዊ ትብብር ማጠናከር በምትችልባቸው ጉዳዮች ዙሪያም መክረዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version