Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የጋናው ኤምፋርማ በኢትዮጵያ በመድሃኒት አቅርቦት ሊሰማራ ነው

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 2 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ኤምፋርማ የተሰኘው የጋናው መድሃኒት አቅራቢ ኩባንያ በኢትዮጵያ በመድሃኒት አቅርቦት መሰማራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ፡፡

ስምምነቱን ከበላይአብ ፋርማሲዩቲካልስ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ጋር መፈራረሙን አስታውቋል፡፡

የኤምፋርማ ዋና ስራ አስፈጻሚ ግሪጎሪ ሬክሰን ስምምነቱ በኢትዮጵያ የህክምናውን ዘርፍ ለማገዝና መድሃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረብ እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version