Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የድሬዳዋ ብልፅግና ፖርቲ የምርጫ ቅስቀሳ ማስጀመሪያ መረሃ ግብር አካሄደ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22፣ 2013 (ኤፍቢሲ) የድሬዳዋ ብልፅግና ፖርቲ የምርጫ ቅስቀሳ ማስጀመሪያ መረሃ ግብር አካሄደ፡፡

በማስጀመሪያ መረሃ ግብሩ ላይ ድሬዳዋ ያላትን መልካዓ ምድራዊ አቀማመጥ በመጠቀም የኢንዱስትሪ፣ የደረቅ ወደብና የንግድ ማዕከል ለማድረግ ፖርቲው እንደሚሰራ አስታውቋል።

የብልጽግና ፖርቲ ከሁሉም በሁሉም ለሁሉም ያሉት የድሬዳዋ ብልፅግና ፖርቲ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ መብራቴ ገብረየስ ፖርቲው በቀጣዩ ምርጫ ለመወዳደር ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ምረጡኝ ቅስቀሳ መግባታቸውን አስታዉቀዋል።

በከተማዋ አራት አቅጣጫዎች የተጀመረው የምረጡኝ ቅስቀሳው ከሰዓት በውይይት እንደሚቀጥል ለማወቅ ተችሏል።

በእዮናዳብ አንዱዓለም

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

 

 

 

Exit mobile version