Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አምባሳደር መለስ ዓለም ከአልጄሪያ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2012(ኤፍ ቢ ሲ) አምባሳደር መለስ ዓለም በናይሮቢ ተቀማጭነታቸውን ካደረጉት የአልጄሪያ አምባሳደር ሰልማ መሊካ ሃዳዲ ጋር ተወያይተዋል።

በውይይታቸውም በናይሮቢ በሚገኙ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጽህፈት ቤቶች በሚካሄዱ ባለ ብዙ ወገን መድረኮች ላይ በቅርበት መስራት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መክረዋል።

አምባሳደሯ በኬንያ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ኤምባሲውን መጎብኘታቸውን በኬንያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

አምባሳደሯ ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ የምክትል የሚሲዮን መሪ በመሆን አገልገለዋል።

Exit mobile version