Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በኢትዮጵያ ከሳዑዲ ዓረቢያ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 15፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል በኢትዮጵያ ከሳዑዲ ዓረቢያ አምባሳደር ሳሚ ጃሚል አብዱላህ ጋር በስደት የሚገኙ ወገኖችን ወደ ሀገራቸው መመለስና በዘላቂነት ማቋቋም በሚቻልበት አግባብ ላይ ተወያይተዋል።
በውይይቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የረጅም ጊዜ የእህትማማችነት ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር በሚያስችሉ የትብብር መስኮች ላይ መክረዋል፡፡
እንዲሁም በዋነኝነት በስደት የሚገኙ ወገኖችን ወደ ሀገራቸው መመለስና በዘላቂነት ማቋቋም ላይ መወያየታቸውን ከሰላም ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፦https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version