Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ወይዘሮ መዓዛ አሸናፊ በኢትዮጵያ ከአሜሪካ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 20 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት መዓዛ አሸናፊ በኢትዮጵያ ከአሜሪካ አምባሳደር ጊታ ፓሲ ጋር ተወያዩ፡፡

በውይይታቸው ወቅት አሜሪካ ለኢትዮጵያ የፍትህ ዘርፍ ማሻሻያ በምታደርገው ድጋፍና እርዳታ ዙሪያ መክረዋል፡፡

አምባሳደር ጊታ ፓሲ የፍትህ ስርአቱን ነጻና ገለልተኛ ለማድረግ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሚደረጉ ጥረቶችን አድንቀዋል፡፡

አያይዘውም በኢትዮጵያ እና አሜሪካ መካከል ያለው አጋርነት እንደሚቀጥል መግለጻቸውን የአሜሪካ ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version