Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የዓለም የፕረስ ነፃነት ቀን እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 26 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም የፕረስ ነፃነት ቀን “መረጃ ለህዝብ ጥቅም በሚል መሪ ሃሳብ” እየተከበረ ነው።

ዛሬ እየተከበረ ባለው የዓለም የፕረስ ነፃነት ቀን የሚዲያ አካላት እና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው ።

ጋዜጠኞች ከስጋት ነፃ ሆነው የሚሰሩበት እና ዜጎች ትክክለኛ መረጃ ማግኘት የሚችሉበትን እድል መፍጠር እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት ሰብሳቢ ትዕግስት ይልማ ተናግረዋል።

መገናኘኛብዙሃን እና ባለሙያዎች በማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ የሚስተዋሉ የጥላቻ ንግግሮችን በመቆጣጠር ሃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

በይስማው አደራው

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version