Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በህንድ የተከሰተው የኮቪድ19 ዝርያ አሳሳሳቢ በመሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል – የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 6፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በህንድ የተከሰተው የኮቪድ19 ዝርያ አሳሳሳቢ በመሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት አሳሰበ፡፡

የዓለም ጤና ድርጅት በህንድ የተከሰተው የኮቪድ19 ቫይረስ አሳሳሳቢ ዝርያ እንደሆነ እና ዓለም አቀፍ ስጋት እየሆነ እንደመጣ ቫይረሱ እስካሁን በ44 ሃገራት እንደተሰራጨ ገልጿል።

ስለሆነም ሁሉም የህብርተሰብ ክፍል ለኮቪድ19 አጋላጭ ሁኔታዎችን በማስቀረት የመከላከያ መንገዶችን በጥንቃቄ እንዲተገብር ማሳሰቡንም ከኢንስቲቲዩቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል ፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version