አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 10 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በቡሌ ሆራ ከተማ በ250 ሚሊየን ብር ወጪ ለሚገነባውን መናሀሪያ የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ፡፡
በምክትል ፕሬዚደንት ማዕረግ የኦሮሚያ ማህበራዊ ጉዳይ ክላስተር አስተባባሪ በአቶ አዲሱ አረጋ የተመራው ልዑክ ቡድን በከተማው ለሚገነባው የተቀናጀ መናሀሪያ የመሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ ስራውን ማስጀመራቸውን ኦቢኤን ዘግቧል፡፡
በኦሮሚያ ትራንስፖርት ባለስልጣን የሚገነባው መናሀሪያው 600 ሰዎችን ማስተናገድ የሚችል ማዕከልና መናፈሻ ስፍራዎችን ያከተተ ሲሆን በ250 ሚሊየን ብር ወጪ የሚገነባ ነው፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!