Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

እኔም ለወገኔ በስዊዘርላንድ የበጎ አድራጎት ማህበር በአጣዬ አካባቢ ለተፈናቀሉ ዜጎች ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) እኔም ለወገኔ በስዊዘርላንድ የበጎ አድራጎት ማህበር በአጣዬ አካባቢ ለተፈናቀሉ ዜጎች ድጋፍ አድርጓል፡፡

ማህበሩ በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ዞን በኤፍራታና ግድም፣ በቀወት፣ በአንጾኪያ ገምዛ ወረዳዎች እና በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን አዋሳኝ አካባቢዎች በደረሰው ውድመት ንብረታቸው ለወደመባቸውና ለተፈናቀሉ ንጹሃን ዜጎች የሚሆን 715 ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡

ከዚህ በፊት ማህበሩ ለታላቁ የህዳሴ ግድብ የ30 ሺህ ዶላር ቦንድ እንዲገዛ ማስተባበሩ ይታወሳል፡፡

በሀበነዮም ሲሳይ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version