Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የስልጤ ዞን ማህበረሰብ ለሴቶች የሚሰጠውን የጊስትነት ማእረግ ከ500 ዓመት በኋላ ለወ/ሮ ሙፈርያት ከሚል ሰጠ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)የስልጤ ዞን ማህበረሰብ ለሴት ልጅ የሚሰጠውን የመጨረሻውን “የጊስቲነት” ማዕረግ ከ 500 ዓመታት በኋላ ለወይዘሮ ሙፈርያት ከሚል ሰጥቷል፡፡

የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈርያት ከሚል በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክትም፥ ባህላዊ እሴቶች ለትውልድ ግንባታ ብሎም ለሀገር ግንባታ ትልቅ ትርጉምና ጠቀሜታ አላቸው ብለዋል።

በተጨማሪም ሚኒስትሯ፥ ‘‘ ላልተገደበው ፍቅራችሁና አክብሮታችሁ እጅግ አመሰግናለሁ’’ ብለዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version