Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ለጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የድምፅ መስጫና ሌሎች ቁሳቁሶች ድሬዳዋ ደረሱ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በመጪው ሰኞ ለሚካሄደው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የድምፅ መስጫና ሌሎች ቁሳቁሶች ድሬዳዋ መድረሳቸው ተገለፀ፡፡
በብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የድሬዳዋ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ዚያድ ያሲን በምርጫ ክልሎቹ ዛሬ የደረሱት የምርጫ ቁሳቁሶች ከነገ ጀምሮ እንደሚሰራጩ ተናግረዋል፡፡
በአጠቃላይ በድሬዳዋ በ259 የምርጫ ጣቢያዎች ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሁለት ለድሬዳዋ አስተዳድር ምክር ቤት ደግሞ 47 እጩዎች ይወዳደራሉ ፡፡
በሳራ መኮንን
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version