Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የአዲስ አበባ ፖሊስ ፖሊሳዊ የደንብ ልብስና ዓርማ መቀየሩን ምክንያት በማድረግ የማብሰሪያ መርሀ-ግብር አዘጋጀ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ፖሊስ ፖሊሳዊ የደንብ ልብስና ዓርማ መቀየሩን ምክንያት በማድረግ የማብሰሪያ መርሀ-ግብር ሊያካሂድ መሆኑን ገለፀ፡፡
ይህን ተከትሎ በዕለቱ ልዩ ልዩ መርሃ ግብሮች የሚከናወኑ በመሆኑ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 6 ሰዓት ድረስ የተወሰኑ መንገዶች ለትራፊክ ዝግ ይሆናሉ ነው የተባለው፡፡
በዚህም መሰረት ከኡራኤል ወደ መስቀል አደባባይ፣ ከኦሎምፒያ ወደ መስቀል አደባባይ፣ከ4ኛ ክፍለ ጦር/ጥላሁን አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ ፣ከሀራምቤ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ፣ከለገሃር ወደ መስቀል አደባባይ፣ከብሄራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱና በተጠቀሱት አካባቢዎች የሚገኙ መጋቢ የውስጥ ለውስጥ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ መሆናቸው ተገልጿል፡፡
አሽከርካሪዎችም አማራጭ መንገዶችን በመጠቀም የተለመደ ትብብራቸውን እንዲያደርጉ ጥሪ ማቅረቡን ከአዲስ አበባ ፖሊስ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version