Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ሆንግ ኮንግ ከእንግሊዝ የሚደረጉ በረራዎችን በሙሉ አገደች

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 22 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ሆንግ ኮንግ ከእንግሊዝ የሚደረጉ በረራዎችን በሙሉ ማገዷ ተሰማ፡፡

ሃገሪቱ እገዳውን ያደረገቹ አዲስ (ዴልታ ) ዝርያ ያለው የኮቪድ 19 ቫይረስ በእንግሊዝ ከመከሰቱ ጋር ተያይዞ መሆኑ ታውቋል፡፡

ሃገሪቱ ከእንግሊዝ ወደ ሆንግ ኮንግ የሚደረግ ማንኛውም አይነት በረራ ለአዲሱ ኮቪድ 19 ዝርያ ተጋላጭ እንደሚያደርግ ነው የገለፀችው፡፡

ይህን ተከትሎም ከሃምሌ 1 ጀምሮ ከእንግሊዝ የሚደረግን በረራ ማገዷን አስታውቃለች፡፡

እገዳው ከእንግሊዝ ወደ ሀገሪቱ በሚገቡ መንገደኞች ላይ ተፅዕኖ ያሳድራል ነው የተባለው፡፡

ምንጭ፡- ቢቢሲ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version