Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጃይካ የኢትዮጵያ የቆዳ ምርቶች በአሜሪካ እና አውሮፓ ገበያ ያላቸውን ተቀባይነት ለመጨመር ድጋፍ እያደረገ ነው

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 23 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የጃፓን ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት (ጃይካ) የኢትዮጵያ የቆዳ ምርቶች በአሜሪካ እና አውሮፓ ገበያ ያላቸውን ተቀባይነት ለመጨመር ድጋፍ እያደረገ ነው፡፡

ለዚህ እንዲረዳም ለአንድ ጫማ ፋብሪካ እና አምስት የቆዳ ቦርሳ አምራቾች ቴክኒካዊ ድጋፍ ስልጠና እየሰጠ ነው፡፡

ስልጠናው ፋብሪካዎቹ የምርቶቻቸውን ጥራትና ንድፍ ለማሳደግና ለማዘመን እንዲያስችላቸው ያለመ መሆኑን ከጃይካ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

ይህም ፋብሪካዎቹ ምርቶቻቸው በአሜሪካና አውሮፓ ገበያ ያላቸውን ተፈላጊነት ለመጨመር የሚያስችል መሆኑም ተገልጿል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version