Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የአዲስ አበባ ስታዲየም የዕድሳት ስራ ተጀመረ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 30፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)የአዲስ አበባ ስታዲየም የዕድሳት ስራ በዛሬው ዕለት ተጀምሯል።
የአዲስ አበባ ስታዲየምን እድሳት ለማድረግ ከሁለት ሳምንት በፊት የውል ስምምነት መደረጉ ይታወሳል።
በውሉ መሠረትም የእድሳት ስራው ዛሬ ተጀምሯል።
ዕድሳቱ በቅድሚያ ካፍ የሰጣቸውን አስተያየቶች መሠረት አድርጎ የሚሰራ ሲሆን፥ የመጫወቻ ሜዳው ፣ የመልበሻና የመታጠቢያ ክፍሎች ፣ የተመልካች መፀዳጃ እና የኤሌክትሪክ እና የጽዳት ስራዎችን የሚያካትት ይሆናል።
የእድሳት ስራውን ፍሬንድስ ኢንጅነሪንግ አማካኝነት እንደሚሰራ ከስፖርት ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version